የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እና ሌሎች አመራሮች የክፍለ ከተማ አስተዳደሩን ሕንጻ እድሳት ያለበትን ደረጃ ምልከታ አድርጓል፡፡ በምልከታው ላይ የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወልዴ ወገሴ እንደተናገሩት በክፍለ ከተማው ከተጀመሩ ፕሮጀክቶች መካከል የክፍለ ከተማውን ሕንጻ ያለበት ደረጃ ለአገልግሎት ምቹ የማድረግ መሆኑን ገልጸው በአጭር ጊዜ በተሻለ ፍጥነትና ጥራት በማጠናቀቅ መሰራት እንደሚገባ ተናግረዋል፡፡