አስተዳደሩ በ3 ወራት በንቅናቄ እየተከናወኑ የሚገኙ የሴቶችና የወጣቶች የስራ ዕድል ፈጠራ ፣ የከተማ ግብርናና የሌማት ትሩፋት ተግባራት ፣ የታላቁ ህዳሴ ግድብ የገቢ አሰባሰብ ፣ የኑሮ ውድነት ለማረጋጋት የተከናወኑ ተግባራትን ፣ የገቢ አሰባሰብ ከክፍለ ከተማና ከወረዳ አመራሮች ጋር ገምግሟል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የጉለሌ ክፍለ ከተማ ብልጽግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ይከበር ስማቸው እንደተናገሩት በክፍለ ከተማው ሁሉን አቀፍ ለውጥ ለማምጣት ስራዎችን በመደበኛና በንቅናቄ እየተመሩ ይገኛል ያሉ ሲሆን በተለይም የታላቁ ህዳሴ ግድብ የሀብት አሰባሰብ ፣ የገቢ አሰባሰብ ፣ የኑሮ ውድነት ማረጋጋት ተግባራትን ሁሉም አመራር በትኩረት በመምራትና በመገምገም ለውጥ ማምጣት ያስፈልጋል ብለዋል። የክፍለ ከተማው ምክትል ዋና ስራ አስፈጻሚና ስራና ክህሎት ኃላፊ አቶ ሰለሞን ታደሰ በበኩላቸው በንቅናቄ እየተመሩ የመጡ የስራ ዕድል ፈጠራና የከተማ ግብርና ስራዎቻችን በመጠናቀቅ ላይ የሚገኙ በመሆኑ ለስራዎቹ ትኩረት በመስጠት ሁሉንም በ100 ፐርሰንት አፈጻጸም በመጨረስ ኢንተርፕራይዝ ማደራጀት ፣ ስልጠና መስጠተ ላይ በትኩረት መስራት ያስፈልጋል ብለዋል።
በክፍለ ከተማው በ2ኛው ዙር ከሚለሙ የወንዝ ዳርቻ ፕሮጀክት የአዲስ ለአዲስ የወንዝ የልማት ፕሮጀክት ተነሺ ለሆኑ የህብረተሰብ ክፍሎች መካከል የምትክ ቦታ እና ምትክ የቀበሌ ዕጣ የማውጣት መርሃ ግብር ተከናወነ።
ትምህርት ቤቶችን ተተኪ ስፖርተኞችን ማፍሪያ ማዕከላት ማድረግ እንደሚገባ ተገለጸ።
የብልጽግና ፓርቲ ጉባኤ ተሳታፊዎች በአዲስ አበባ ከተማ የተሰሩ ሰው ተኮር ስራዎችን እየጎበኙ ነው።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በንቅናቄና በመደበኛ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ዙሪያ ከክፍለ ከተማና ከወረዳ አመራሮች ጋር ገምግሟል።
የጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በንቅናቄና በመደበኛ እየተከናወኑ የሚገኙ ተግባራት ዙሪያ ከክፍለ ከተማና ከወረዳ አመራሮች ጋር ገምግሟል።
የመማር ማስተማር ስነ ዘዴ ተግባራዊ በማድረግ የነገ ሃገር ተረካቢ ዜጋ መፍጠር እንደሚገባ ተገለጸ።
የጉለሌ ወረዳ 9 አስተዳደር አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመን በካሜራ የተደገፈ ምርጥ ተሞክሮ ማስፋቱ ተገለጸ ።
ምቹ ተቋም ለተሻለ አገልግሎት ፍጥነትና ጥራት !!